"
THE FORMER ETHIOPIAN NAVY MEMORIAL WEBSITE
  • THE FORMER ETHIOPIAN NAVY WEBSITE
  • ገጽ2
  • ገጽ3
  • ገጽ4
  • ገጽ 5
  • ገጽ 6
  • ገፅ 7

 ከቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ባሕር ኃይል እስከ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ልዩ ልዩ ፎቶግራፎች። የብሪታኒያ ባሕር ኃይል አባላት ምፅዋ ባሕር ኃይል መደብ በተገኙ ጊዜ የነበሩ አጋጣሚዎች ነው አንዳንዶቹ ፦ THE  ROYAL  ETHIOPIAN  NAVY  ,  SOCIALIST  ETHIOPIAN  NAVY ( After Emperor Haileslassie Deposed by Military Coup ) PICTURES & ALSO  THE  ROYAL GREAT  BRITAIN  NAVY  OFFICERS  IN ETHIOPIA  AT MASSAWA SEA  PORT ON THE OCCASION  OF NAVY  DAY ( IN 1960S)   .  --  ETHIOPIAN  NAVY  WAS  ESTABLISHED  BY NORWEGIAN  NAVY ; THEN  THE ROYAL  GB  NAVY HAD  SECONDED  ETHIOPIAN  PERSONNEL  TO  ITS BASES  IN  ERITREA TO  PROVIDE  THEM  WITH NAVAL TRAINING.  THE NAVAL COLLEGE , WHERE  ETHIOPIAN  NAVAL  OFFICERS  UNDERTOOK A  52  MONTH PROGRAM  STUDY  WAS  FOUNDED  AT ASMARA IN 1956.

 The Former Ethiopian Navy Commander In Chief ' Rear Admiral Tesfaye B speech In Amharic Jan, 1987GC on the Occasion Of 31st Annual Ethiopian Navy Day

ETHIOPIAN NAVY DRILL TEAM IN 1987 GC (  1979 Ethiopian Calendar )

IN 1987 JANUARY ( Ethiopian Navy Day) , THE ETHIOPIAN NAVY OFF DEPLOYMENT WAR SHIPS & GUN BOATS FORMATION TO SALUTE THE PRIME MINSTER OF ETHIO AT SEA. እንደ ኢትዮ አቆ በ 1979ዓም ግዳጅ ላይ ያልነበሩት የጦር መርከቦች በሰልፍ ሆነው ለጠ/ሚንስትሩ ሠላምታ ሲያቀርቡ

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ቀን እንደ ኢትዮጵያ አቆ በ 1979ዓም ጥር - THE FORMER ETHIOPIAN NAVY DAY & GRADUATION CEREMONY IN 1987 JAN

7 COUNTRIES NATION NAVAL FORCES CELEBERATING NAVY DAY IN ETHIOPIA MASSWA 1974 GC

TEDDY AFRO'S SONG IN ENGLISH ' MOTHERLAND '

 ETHIOPIAN ARMY MARCHING BAND PLAYS UK NATIONAL ANTHEM

 - ' WE ARE ALL ETHIOPIAN,  IN THE SENSE THAT HUMANKIND FIRST ORIGINATED FROM YOUR COUNTRY' ( MRS BERIT REISS- ANDERSEN THE NOBEL PRIZE COMMITEE ANNOUNCER ) ON THE OCCASION OF 2019 NOBEL PRIZE AWARD TO THE ETHIOPIAN PRIME MISTER ' ABIY AHMED '

  የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል መኮንኖች ፎቶግራፎችና  ፤ ዕጩ መኮንኖችን ቀዳማዊ ኃይለሥላሴና ፤ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ሲመርቁና የክብር ዘቡን ሲጎብኙ...…
VARIOUS  PICTURES  OF  THE  FORMER  ETHIOPIAN  NAVY  SENIOR COMMANDING OFFICERS VISITING ABROAD  INCLUDING  OUR COUNTRY ETHIOPIA PREVIOUS  LEADERS

  ETHIOPIAN NAVY DAY MEMORIAL IN 2018 ADDIS ABEBA የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አባት ጦር አባላት '  የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ቀን ' ትዝታ ከ LTV ጋር በመተባበር አዲሱን አመት 2011 ን በደማቅ ስሜት አክብረዋል

 የቀድሞው ጦር ኃይሎች ጀግኖች ምሽት ክብረ በዓል በዋሽንግተን ዲሲ በተደረገበት ወቅት ስለ ባሕር ኃይላችን የምፅዋ ባሕር ኃይል መደብ ስለተደረገው ተጋድሎ ( በ 20 ኪ.ሜትር ምሽግ ተሠራ የሚለው ቃል በ 20 ኪ.ሜትር የ FIRING ZONE ርቀት CALCULATED ነውና ይቅርታ) ምሽጎች የተሠሩት በመደቡ ግቢና በምፅዋ ሆስፒታል ጓሮ ብቻ ነው።

በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው የረጅም ርቀት የሚሳይል ተኩስ ሙከራ የተደረገው በኢትዮጵያ ባህር ሃይል ፈጣን አጥቂ 111ኛ ስኳድሮን ከነበሩት አንዷ በ FMB-163 ጦር መርከብ ነበር

ETHIOPIAN HEROES NIGHT IN WASHINGTON DC USA

  ከዌብሳይቱ ጀርባ የሚታየው ፎቶግራፍ በቅርቡ ፈረንጆች ቀይ ባሕር ጥልቀት ላይ ( SEA BED)  ገብተው በ UNDER WATER CAMERA ያነሱት ፎቶግራፍ ነው 

IF YOU WOULD LIKE TO SHARE THE WEBSITE TO OTHERS, PLEASE CLICK THE FACEBOOK ICON.

ለሌሎች ኢትዮጵያውያን ዌብሳይቱ እንዲታይ ከፈለጉ በስተቀኝ ያለውን የ FACEBOOK አርማ ይጫኑ

    የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል መታሰቢያ  ዓላማ የአገልግሎት ዘመን  ትዝታችንን  በማስታወስ ኢትዮጵያ  ሃገራችን  ባለባሕር በር ሃገር  መሆኗን፤  ኢትዮጵያዊ መጪው ትውልድም ይሁን  አሁንም '  ሕ ወ ሃ  ት  ' ወያኔ በሚዲያው አደንዝዞ ግራ ያጋባውን ሕብረተሰብ  የአሰብ ወደብ ባለቤትነቱን እንዳይረሳና  ወያኔ ከተወገደ  በኋላ መብቱን  እንዲያስከብር  ማስታወሻ  ነው።
እንደሚታወቀው  የባሕር ኃይላችን  ቀይ ባሕራችንን  በማስከበር ረገድ አንድም ጊዜ በውጭ ወራሪ ኃይል ያለመደፈራችን ምክንያት  የባሕር ኃይላችን ብቃት ከአካባቢው ሃገራት የተሻልን በመሆናችን በገሃድ የሚታወቅ ሃቅ ነበር።  እንኳንስ አሁን ወንበዴዎች ሃገሪቷን የባሕር በሯን በዘጉበት
ዘመን ይቅርና በደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት ዘመን የባሕር ኃይላችን ሚና  በቂ የሚዲያ አገልግሎት  ጊዜ ተሰጥቶት ሕዝባችን ምን እያደረግን እንደነበርን የሚያውቀው ነገር አልነበረም። የምድር ጦርና የአየር ኃይል አባላትም ቢሆኑ ስለ ባሕር ኃይላችን ቀይ ባሕርን በማስከበሩ ረገድ የሚያደርገውን ትሩፋት በአጋጣሚ ከአሰብ ምጽዋ ወይም ወደ ሰሜኑ የጦር ግምባር የባሕር  ጠረፍ በሚደረገው ጉዞ ሁኔታ ካላዩ በስተቀር  ብዙም የሚያውቁት ጉዳይ አልበረም።  ኢትዮጵያ በ 36ቱ የዘመናዊው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አገልግሎት ዘመን በውጭ ወራሪ ኃይል ተደፍራ አታውቅም። ሻቢያ በውጭ ሃገራት ተደጋግፎ በሌለው አቅም ሥልጣን ከያዘ በኋላ የነዳጅ ክምችት አላቸው የሚባሉትን '  የሃኒሽ ደሴቶችን ' በየመን ተሸንፎ ሲያስረክብ እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አባል ቁጭቱንና እልሁን ሆድ ይፍጀው ብሎ ዝም አላለም። ኤርትራ ራሷን ችላ የምትገነጠል ከሆነ '"  ደንከል አውራጃና አሰብ ወደብን ጨምሮ ባለቤቱ ቀደም ብሎም በወሎ ክፍለሃገር አውሳ አውራጃ '"  በደርግም ዘመን ደንከል አውራጃ '"  አሰብ ራዝ ገዝ '''  ሆኖ ራሱን የሚያስተዳድር ክልል ነበር።  መፃኢው ተመራጭ መንግሥት የኢትዮጵያን ሕልውና ለማረጋገጥ ቆራጥ ሆኖ የጥንቱም ማስረጃ በተባበሩት መንግሥታት ጽ/ ቤት አለና በሰላማዊ መንገድ የማስከበር ታላቅ የታሪክ አደራ ኃላፊነት አለበት። ድኅነታችን በገዛ ወደባችን የወደብ ቅኝ ተገዢ መሆናችን የኢኮኖሚ ምሁራን ይናገራሉ ፤ ፪ቱም ወደቦቻችን በእኛ ቁጥጥር ሥር በነበሩ ዘመን ግለሰብም ይሁን የመንግሥት ፋብሪካዎችና ልዩ ልዩ ተቋማት ከውጭ ሃገር ለሚያስገቡት ሸቀጥና ንብረት ለወደቦቹ የሚከፍሉት በውጭ ምንዛሪ '  በዶላር '  ሳይሆን በራሳችን "  በብር "  ነበርና ብራችንም  በዓለም ሃገራት ኃይልና ዋጋም ነበረው።  ያለባሕር በር ሕ ወ ሃ ት ለሠራው የብሔር ፌዴራሊዝም ለክልል ግንጠላ የምትታገሉ የዘመኑ እንቆቅልሾች ሕልማችሁ እውን ቢሆን የወደብ ባርነቱ ቀንበር ይብስባችኋል።  ኢትዮጵያዊነት አንድነትና ኅይል ነው ፤
​ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
  አሜን። 

የኢትዮጵያ  ባሕር  ኃይል  አባላት  "በሕይወት  ያሉና "፡ እናት  ዓለም ኢትዮጵያን  የባሕር  ድንበሯን  ሲጠብቁ ና  ሲያስከብሩ የወደቁ አባሎች ፎቶግራፎች.   THE  FORMER  ETHIOPIAN  NAVY   RATING   MAMBERS  ALIVE  &  FALLEN   ON  LINE   OF  DUTY  DUE  TO   THE  MOTHERLAND  ETHIOPIA TERRITORIAL  INTEGRITY  

PAUSE የሚለውን ቃል በመጫን አቁመው መመልከት ይችላሉ

10  COMMANDMENTS  OF  THE  ETHIOPIAN  NAVY  DAMAGE  CONTROL WAS


1- KEEP YOUR SHIP WATER TIGHT

2- DO NOT VIOLATE MATERIAL CONDITION

3- HAVE CONFIDENCE IN YOUR SHIPS ABILITY TO WITHSTAND DAMAGE

4- KNOW YOUR WAY AROUND- EVEN IN THE DARK

5- KNOW HOW TO USE AND MAINTAIN DAMAGE CONTROL EQUIPMENT

6- REPORT DAMAGE TO NEAREST DAMAGE CONTROL REPAIR STATION

7- KEEP PERSONAL ARTICLES PROPERLY SECURED

8- PRACTICE PERSONAL DAMAGE CONTROL; PROTECT YOURSELF SO YOU CAN PROTECT YOUR SHIP


9- TAKE EVERY POSSIBLE STEP TO SAVE THE SHIP AS LONG AS A BIT OF HOPE REMAINS

10- KEEP COOL, DON'T GIVE UP THE SHIP




ከሕንድ የባሕር ኃይል ጦር መርከብ ሚዚየም ላይ ግለሰብ በሞባይል ቴሌፎን ቀርጾ ፌስቡክ ላይ ጭኖት ያገኘሁት ሲሆን ሁሉም ነገሯ አንድ ዓይነት OSA CLASS MISSILE LOUNCHING  የጦር መርከብ ስለሆነች ለእኛም ትዝታ፦

ኤርትራ ከተገነጠለች አሰብ ወደብም ሆነ ደንከል አውራጃ ከደቡብ ቀይ ባሕር ጋር ቀሪነቱ የኢትዮጵያ ነው

Picture

ክቡር ዶክተር አምባሳደር ካሣ ከበደ፡ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አባላት፡ በየመን ሃገር ለ 11 ዓመታት ሲንገላቱ በቆዩበት ዘመን በተቻላቸው መጠን ሁሉ ታግለው እያንዳንዱ የባሕር ኃይል እስከነቤተሰቡ ወደ አሜሪካን ሃገር እንዲዛወሩ ሃሳባቸውና ጥረታቸው ተሳክቶላቸዋል። በርግጥም ክቡር ኮማንደር አሠፋ ሠይፉም የተቻላቸውን ሁሉ ጥረት ማድረጋቸው ከእያንዳንዱ የባሕር ኃይል ታላቅ ምሥጋና ያቀርባሉ። ክቡር ዶክተር አምባሳደር ካሳ ከበደ፤ ክቡር ኮማንደር አሠፋ ሠይፉ፤ እንዲሁም በዚህ የተቀደሰ ተግባር የተቻላችሁን ጥረት ያደረጋችሁ ሁሉ፡ ፈጣሪ የኢትዮጵያችን አምላክ ረጅም ዕድሜና ጤና እንዲሰጥልን ፀሎታችን ነው።
Picture
Picture
  •  ክቡር ካፒቴን መርሻ ግርማ ፡ ከባሕር ኃይላችን ሲንየር የባሕር ኃይል መኮንኖች አንዱ ሲሆኑ፡ እውቀታቸውን ከድፍረታቸው ጋር በራስ የመተማመን ባሕርያቸው ጋር ከምክትል የጦር መርከብ አዛዥነት እሰከዋና አዛዥነት ሃገራቸው ኢትዮጵያን በጀግንነት አገልግለዋል። በባሕር ኃይል አባልነት ከተቀጠርን ጊዜያት አንስቶ በ1970 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር የነበሩት አለቆቻችን ሲናገሩ፡ ጠላት የሻቢያ ጦር መላውን ኤርትራ ከአሥመራና ከምጽዋ በስተቀር በተቆጣጠረበት ወቅት፡ በምጽዋ አካባቢ የነበረው ጦር አፈግፍጎ በኢትዮጵያ የባሕር ኃይል መደብ በተጠጋበት ወቅት የባሕር ኃይላችንን የእግረኛ ጦር በማስተባበር መደቡ እንዳይያዝ የጦር መርከቦች የመድፍ ድጋፍ እየሰጡ እንዲዋጉ ሌትና ቀን በጀግንነት የመሩ እነደነበሩ በወቅቱ የነበሩት ይመሠክራሉ።

  • ከሃገር መከላከያና ከዋና የልዩ ልዩ ክፍል አዛዦች በአመራራቸው ላይ ተጽእኖ ሊያደርጉባቸው ሲሞካክሩ፡ ለማይመለከታቸው ነገር ሁሉ ተገቢ መልስ በመስጠት አመራራቸውን በተግባር ያሳዩ ውድ የኢትዮጵያ ሃገራችን ጀግና መኮንን ናቸው። በነበረው ስርአት ደስተኛ ባለመሆናቸውና ያልመሰላቸውን ነገር በድፍረት  ያለመቀበላቸው፡ ወደሚቀጥለው ማእርግ እንዲተላለፉ ያለመደረጉ፡ በተለይም የ1970 ው የአመራር ገድል የርሳቸው አመራር ሆኖ ሳለ፡ ሌሎች በሹመት ላይ ሹመት ሲደራረብላቸው የርሳቸውን ገድል ያዩ ሁሉ አለቆቻችን የሁልጊዜ ርእሰ ጉዳይ እንደነበር አይረሳኝም። ለወታደራዊ ከፍተኛ መኮንነታቸው ለተሰጣቸው ከባድ ኃላፊነት ከፍተኛ ጥንቃቄና በራሳቸው የሚተማመኑ ከመሆናቸው የተነሳ፡ ከምጽዋ ባሕር ኃይል መደብ ለሥራ ጉዳይ ወጥተው ሲመለሱ፡ በዋናው በር ላይ ያሉትን ዘቦች፡ እኔ እየነዳሁ ያለሁት መኪና መፈተሽ አለበት፤ ምናልባትም በጠላት ታፍኜ የባሕር ኃይሉ ግቢና በአካባቢው ያሉ የቆሙ ጦር መርከቦች ላይ ጠላት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በማለት ይናገራሉ፤ የጥቂት ስህተት ነገር፡ በጠላት መጠቃት እንደሚያመጣ ይናገሩና የሚያሳስቡና ባለግርማ ሞገስ ከፍተኛ መኮንን ናቸው።  ረጅም እድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ፡ ውድ ካፒቴን መርሻ ግርማ።

Picture
ክቡር ኮማንደር ማቴዎስ መኮንን ከባሕር ኃይላችን የማሪን ኢንጂነሪንግ ሲንየር መኮንኖች አንዱ ናቸው። ለሰባት አመታት ተኩል ባገለገልኩበት የ8ቱም ፈጣን አጥቂ ጦር መርከብ 111ኛ ስኳድሮን የማሪን ኢንጂነሪንግ ኮማንደር ሲሆኑ፡ የጦር መርከቦቹ ምንጊዜም ለግዳጅ ብቁ እንዲሆኑ፡ ከየጦር መርከቦቹ አባሎችን መርጠውና ሞባይል ቲም በማቋቋም የሶቪየት ሥሪት የሆኑትን የጦር መርከቦች ጥገና ሲያደርጉ ዕውቀታቸውን ሳይሸሽጉ በቲዎሪም ይሁን በተግባር ክልብ በሆነ ጥረት የሚያደርጉትን ሁሉ አብረዋቸው የሚሠሩት የማእርግ ጓደኞቼ ሁሉ በየዕለቱ ሲናገሩ የምንሰማው ሃቅ ነበር።


በተለይም የሶቪየት ጦር መርከቦች ኢንጂን EXPIRED DATE የተመደበለትና በአጋጣሚ ብልሽት ቢያጋጥመው እንኳን፡ እንደ ምራባውያኑ መለዋወጫ ተገጥሞለት እንደገና በሥራ ላይ እንዳይውል የተደረገ ስለነበር፡ ሁኔታው ከሚያሳስባቸው ቀዳሚ መኮንኖች አንዱ ስለነበሩ፡ አስታውሳለሁ በጦር መርከብ 162 ላይ GEAR BOX ላይ ችግር አለ በማለት SEALED ሆኖ የተገጠመውን ኢንጂን ከሌሎች የጦር መርከቦች ተፈታቶ ሜዳ ላይ ተቀምጦ ከነበሩት አስቸጋሪ የነበረው ውስብስብ በመፈታታት ለመርከባችን ጥገና አድርገው በብዙ ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣ የነበረውን ዋጋ ከአስተባበሩት የጥገና ቡድን ጋር ዓላማቸውን አሳክተዋል። ቀደም ብሎ ሁሉም የሶቪየት ጦር መርከቦች ነዳጃቸው በውድ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ስለነበር የሚገዛው፡ እንደሌሎቹ ከመራባውያን የተገዙት የጦር መርከቦች አሰብ ከሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ ነዳጃቸውን እንዲጠቀሙ፡ ከሌሎች መኮንኖች ጋር በመሆን ሁኔታውን አጥንተው ሃገራችንን ከኪሳራ ያዳኑና የሙያ አጋሮቻቸውና የማዕርግ ጓደኞቻችን፡ እውቀታቸውን በማካፈልም ሆነ ጉልበታቸውን ጭምር አብረው በመሥራት በተግባር  ሁልጊዜ በሚያደርጓቸው ከልብ የሆነ ትጋት፡ በማድነቅና በማክበር የሚያመሰግኗቸው ውድ የባሕር ኃይላችን ከፍተኛ መኮንን ናቸው።

 ---"""   ሌላው የእርሳቸው ትሩፋት፡ የባሕር ኃይላችን ጦር መርከቦች መደብ ወደ ዳሕላክ፤ ናኩራ ከተዛወረ በኋላ፡ በደሴቲቱ ላይ የውሃ ግድብ ባለመኖሩና በአካባቢው ያለው የባሕር ኃይልና የምድር ጦር ሠራዊት የውኃ ችግር በጣም የበረታበት ቦታ ስለሆነ፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከእስራኤል ሃገር የቀይ ባሕርን የጨው ውኃ ወደ ንጹሕ ውኃ የሚለውጥ ( DISTLLING PLANT) ታላቅ ፕሮጀክት እቅድን በተመለከተ፡ ለቀናት ብቻ እዚያው እስራኤል ሃገር ከውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ቴክኒሺያኖች ጋር ሄደው በእስራኤሎች በተደረገላቸው የጥቂት ቀናት ማብራሪያ ብቻ፡ ወደ ውድ ሃገራቸው እንደተመለሱ የ DISTLLING PLANT ቀደም ብሎ በሃገራችን ያልነበረ ቢሆንም፡ አብረዋቸው ለማብራሪያው እስራኤል ሃገር የነበሩት፡ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሠራተኞች ግዙፉ ፕሮጀክት ግራ አጋብቷቸው፡ ኮማንደር ማቴዎስን የሚሳካ ይመስለዎታልን ጥያቄ ሲአያስከትሉ፡ በአጋጣሚ የመጣው መሣሪያ ሁለት ቢሆንም፡ አንደኛው በንግድ መርከብ ጭነት ሲመጣ በማዕበል የተጎሻሸመና የተጎዳ ቢሆንም፡ ኮማንደሩ ባላቸው የዕውቀትም ይሁን የራስ ተነሳሽነት ፅናት ተደማምሮ መሣሪያው እንዲሠራና  ሁሉም ነገር ተሳክቶ የሠራዊቱንም ይሁን የአካባቢውን ሕዝብ የውኃ ፍላጎት አሳክተዋል። ኮማንደሬ ረጅም  ዕድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ """"
።