"
THE FORMER ETHIOPIAN NAVY MEMORIAL WEBSITE
  • THE FORMER ETHIOPIAN NAVY WEBSITE
  • ገጽ2
  • ገጽ3
  • ገጽ4
  • ገጽ 5
  • ገጽ 6
  • ገፅ 7

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል የሴት መርከበኞች ( WAVES) እና መኮንኖች ነበሩት

22/6/2016

0 Comments

 
Picture
0 Comments

የዶጋሊ 100ኛ ዓመት በዓል ሲከበር አሉላ ፓንክረስት ስለራስ አሉላ አባ ነጋ ደራሲ ማሞ ውድነህ የገጠሙትን በቃሉ አንብቦ ነበር Click here to comment & Read

20/5/2015

0 Comments

 
0 Comments

MY  CV LAST PAGE

5/12/2014

0 Comments

 
Picture
0 Comments

PRESIDENT  MENGISTU H/M WAS SAILING ON BOARD ENS ETHIOPIA MASSAWA TO ASSAB  ( click here to comment & Read)

12/8/2014

0 Comments

 
ሪር አድሚራል ተስፋዬ ብርሃኑ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ዋና አዛዥ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ከምፅዋ ወደ አሰብ በተጓዙ ወቅት ስለቀይ ባሕር በጦር መርከብ ኢትዮጵያ ላይ ሆነው ገለጻ ሲያደርጉ
Picture
0 Comments

ዘርዓይ ደረስ  ሮማ፤  አሉላ  ዶጋሊ Click here to comment & Read

7/6/2014

1 Comment

 
Picture
የጀግናው ዘርዓይ ደረስ እናት በጀግናው ልጃቸው በተሰየመችው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ጦር መርከብ ላይ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት( እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1950ዎቹ ዓም

Picture
ራስ አሉላ (አባ ነጋ) የደርቦሾችን ( የግብጾችን) መሪ ፓሻውን በጦርነቱ ላይ ከገደሉ በኋላ የፓሻውን ዩኒፎርም ለብሰው ለማስታወሻ የተነሱት ፎቶግራፍ ነው

የራስ አሉላ እንግዳ( አባ ነጋ) የዶጋሊ ጀግንነት ተጋድሎ በአውሮፓ ዜናው እንደተሰማ ጎብኚዎች እርሳቸውን ለማየት በዚያን ዘመን አጠራር ሃማሴን አሁን አሥመራ ድረስ ይመጡ ነበርና፡ አንድ አውሮፓዊ ፡ አሥመራ እንደደረሰ ለራስ አሉላ ልዩ ስጦታ ይዤ መጥቻለሁና እባካችሁ አቅርቡኝ ብሎ በጠየቀው መሠረት ከአስተርጓሚ ጋር ይቀርባል።  ራስ አሉላ ቁመታቸው አጭር ስለነበር ጎብኚው እፊታቸው ቀርቦ ግራ ተጋባ፡ ለአስተርጓሚው እኔ የመጣሁት ራስ አሉላን ለማየትና ስጦታ ላበረክት ነውና እባክህ የታሉ በማለት ጠየቀ፡ እኚህ ናቸውኮ ብሎ አስተርጓሚው ሲነግረው አላመነም። እኔኮ ራስ አሉላ ማለት ግዙፍ ሰው ነበረ የምጠብቀው ብሎ ተናገረ። አስተርጓሚው ሁኔታውን ተርጉሞ ለራስ አሉላ እንደነገራቸው ወዲያውኑ ፡ ንገረው!!!  ግማሹ ሰውነቴ መሬት ውስጥ ነው ያለው ብለው ተናገሩ፤ ጎብኚውም ስጦታውን ሲያበረክት ፡ ተከፍቶ ሲታይ አዲስ ጠመንጃ ነበር። ራስ አሉላም በጦርነት ከማረኩት ልዩ ጠመንጃዎች አንዱን ሸልመው ብልህነታቸውን በጥበብ ነግረው በጥበብ ሸልመው አሰናብተውት እንደነበር ቀደም ካሉ መጻሕፍት አንብበናል።


Picture

ስለ የኢትዮጵያ ጀግናው የሃማሴን ተወላጁ ዘርዓይ ደረስ ታሪክ ሲነገር በሻቢያ ዘመን ኤርትራ ውስጥ ለነበሩ ወጣቶች እንግዳ ነገር ነው። ምክንያቱም ሻቢያ ገና ከጀብሃ ከሚባሉት የአረብ ፈላሻዎች ተገንጥሎ ከመውጣቱ አስቀድሞ ምሥረታው በጣሊያን ባንዳ አሽከሮች (ሹምባሽ) በነእድሪስ አወቴ ሱዳን ውስጥ በሶርያውያን ረዳትነት ሲመሠረት ፀረ ኢትዮጵያዊነት እነደነበር አያውቁምና።
ሻቢያ ለኤርትራ ሕዝብ ልክ እንደወያኔ አዳዲስ የወሬ ፈጠራ ታሪክ በመመሥረት ኢትዮጵያዊ ስሜት እንዳይኖራቸው አዳዲሱን ትውልድ ቅኝ፡ገዢዎቻቸው በባርነት በሰጧቸው ስም የታሪክ ክህደት የተነሳ፡ የዚያን አካባቢ የጥንት ስም ማለትም " ባሕረ ነጋሲ ወይም ባሕረ ነጋሽ "  የሚለው ስም እንዲጠፋ አድርገዋል። ስለራስ አሉላ እንዳይነሳ ደርግ የፈጠረው እንጂ በታሪክ ራስ አሉላ የሚባል ነገር የለም በማለት ናፅነት እንዳሉት ሳይሆን አዲስ ለፈጠሩት ስደተኛ ትውልድ አስተምረዋል።
ስለዘርዓይ ደረስ ሲነሳ አንድ ግለሰብ በማለት አጥላልተዋል። ዘርአይ ደረስ ግን ባርነት የማይስማማው ኢትዮጵያዊ ሆኖ በጠላት የሙሶሊኒ ኢጣሊያን ወታደር ሶላዳቶዎች በረገጧት ሰንደቅ ዓላማችን ውርደት እነደነሻቢያ-ወያኔዎች ሳይክድ፡ ስለሃገሩ ኢትዮጵያ ፍቅር ማድረግ የሚገባውን በጀግንነት ተወጥቷል።


ኢትዮጵያ ሃገራችን በግርማዊ ጃንሆይ ዘመነ አጼ ዮሓንስ 4ኛ ስትስተዳደር ፡ ቅኝ ገዢዎች እንዲሁም ደርቡሾች( ግብጾች ) የአባይ ወንዝ መነሻ የሚያጠቃልል ካርታ ለመመሥረት ቋምጠው ተደጋጋሚ ጥቃት ቢያደርሱም በፍጹም አልተሳካላቸውም ነበር። በኤርትራ አካባቢ ያለውን መላ ክልል እንዲያስተዳደሩ የተሾሙት ራስ አሉላ አባ ነጋ ተደጋጋሚ የደርቡሾችን ( የግብጾችን ) ጥቃት በተለይም በጉራዕና በጉንዳጉዲ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ 1875 እስከ 1876 የግብጹን የጦር መሪ ( ፓሻ) ማርከውና ገድለው ለመታሰቢያ የፓሻውን ዩኒፎርም ለበሰው ፎቶግራፍም ተነስተዋል።  በከረንና ኩልፊት  እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1885 የግብጽ ማህዲስቶች ወይም ደርቡሾችን ድል አድርገዋል። ከማሕዲስቶች ጋር ጦርነት ገጥመው በማካሄድ ላይ እያሉ ጣሊያኖች ምፅዋን ተቆጣጥረው ስለነበር፡ ጦርነቱን በድል አጠናቀው ሳለ ፊታቸውን ወደ ምፅዋ ባዞሩ ዘመን፡እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1887 ዓም ጣሊያኖች ጭራሽ መላውን ኤርትራ ለመያዝ ከምጽዋ ተነስተው ሲገስግሱ ራስ አሉላ ዶጋሊ ላይ የጣሊያን ጦር ሲደርስ ድንገተኛ ማጥቃት ሰንዝረው ከ500 በላይ ጣሊያኖችን በመማረክና በመግደል የድሉ ባለቤት እንደነበሩ፡ የኢትዮጵያ ታሪክ መዛግብት ላይ በተደጋጋሚ ተጽፏል።
በኋላም ደርቡሾች መተማ ላይ ኃይለኛ ጦርነት በከፈቱበት ወቅት እራሳቸው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አጼ ዮሕንስ ዘምተው በጦርነቱ ላይ ተሰውተዋል። አጼ ዮሓንስ ከአረፉ በኋላ፡ የኢትዮጵያ ጦር ኃይል የመሪው መሞት በድንጋጤ በመዳከሙ፡ የጣሊያን ጦር መላውን ኤርትራ በመቆጣጠር የጣሊያን መንግሥት ቅኝ መሬት አደረገው። ጣሊያኖች በእምዬ ምኒልክ በ1896 ዓም አድዋ ላይ በተሸነፉ በ40ኛው ዓመት እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1928 ዓም መላውን ኢትዮጵያ ወረሩ ፡ ከዚያም በዘረፋ የራሳቸው ታሪክ ያልሆኑትን የሃውልት ሌብነት ሲያደርጉ ከአክሱም አንድ ሃውልትና፡ ለገሃር የነበረውን የይሁዳ አንበሳ ሃውልት ነቅለው ጣሊያን ዋና ከተማ " ሮማ " ላይ ተከሉት።


ከዕለታት በአንዱ የጣሊያን አመታዊ በዓላቸው ቀን ፡ ጀግናው ዘርዓይ ደረስን ከአሥመራ በጣሊያን ቋንቋ አስተርጓሚነት ወስደውት እዚያው ስለነበር፡ የሃገሩን የአርበኝነት ዩኒፎርም እስከነ ሙሉ ትጥቁ ጎራዴውን ጨምሮ ለብሶ በዓሉ ቦታ ላይ እንዲገኝ አደረጉ። ከዚያም የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን መሬት ላይ አንጥፈው እየረገጡና ምራቃቸውን እየተፉ ሲረማመዱበት ጀግናው ወጣቱ ዘርዓይ ደረስ መታገስ አልቻለም፤ አጠገቡ ካሉት በመጀመር የጣሊያን ወታደሮች አንገት መቀንጠስ ጀመረ፤ ጣሊያኖች እግሬ አውጪኝ ሽሽት ጀመሩ፡ ዘርዓይ ደረስን የሚያስቆመው የሰው ክንድ እንዳልሆነ አወቁ፡ ወዲያው ተኩሰው እግሩን አቆሰሉት። ወደ እስር ቤት አስገብተውት ቢሆንም ጀግንነቱ በመላው ጣሊያን ሃገር ገነነ። ሆስፒታል አስገብተው በሕክምና ሂደት ላይ ሳለ፡ ኢትዮጵያ ሃገራችን ድል እንደተቀዳጀች፡ ሙሶሊኒ በገዛ ሕዝቡ ተገድሎ አዲስ የጣሊያን መንግሥት ስለተመሠረተ፡ ግርማዊ ጃንሆይ አጼ ኃይለሥላሤ፡ በምርኮና በግዞት ጣሊያን የወሰዳቸውን አርበኞች ሲያስመልሱ፡ ጣሊያኖች ሆን ብለው ይህንን ወጣት ጀግና ገድለው ታሞ ሞተ በማለት ሕይወቱን ቀጥፈውት እንደነበር የኢትዮጵያ ታሪክ ጻሕፍትና የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት መምሕራኖች በተደጋጋሚ በመዘከር የዘርዓይ ደርስን ትሩፋት ነግረውናል፤ አስተምረውናል። የጀግንነት ስሙ ለዘለአለም ሲታወስ ይኖራል፡፤











Picture
ይሕች የጦር መርከብ በዘመነ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃያለሥላሤ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተገዝታ በጀግናው ዘርዓይ ደረስ ስም ተሰይማ የነበረች የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል የጦር መርከብ ናት።

1 Comment

 የወያኔ ፋሽዝም ጠቅላይ ወንጀል ሚንስትር መለስ ዜናው በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል የጦር መርከቦችና የባሕር በራችንን አዘጋግ ወንጀሉ፦ (  Click here to comment)

27/5/2014

0 Comments

 
______7_.wps
File Size: 30 kb
File Type: wps
Download File

0 Comments

የምፅዋ  ጦርነት  ፲፱፻፹፪ እንደ ኢትዮጵያ አቆ የካቲት  እውነታው

4/5/2014

1 Comment

 
1 Comment

የኢትዮጵያ  ባሕር  ኃይል  አባላት  በዘመነ ቀዳማዊ  ኃይለሥላሤ  ከነበሩት ከሰማሁት   እንዳቀናበርኩት

30/3/2014

0 Comments

 
0 Comments

ክፍል ፩  ከባሕር  ኃይላችን  ትዝታ ( የከባድ ጦርነት ውሎ) ፍሬሠናይ ከበደ  ( Click here to comment & Read)

4/3/2014

0 Comments

 
0 Comments
Picture
Picture
  •  ክቡር ካፒቴን መርሻ ግርማ ፡ ከባሕር ኃይላችን ሲንየር የባሕር ኃይል መኮንኖች አንዱ ሲሆኑ፡ እውቀታቸውን ከድፍረታቸው ጋር በራስ የመተማመን ባሕርያቸው ጋር ከምክትል የጦር መርከብ አዛዥነት እሰከዋና አዛዥነት ሃገራቸው ኢትዮጵያን በጀግንነት አገልግለዋል። በባሕር ኃይል አባልነት ከተቀጠርን ጊዜያት አንስቶ በ1970 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር የነበሩት አለቆቻችን ሲናገሩ፡ ጠላት የሻቢያ ጦር መላውን ኤርትራ ከአሥመራና ከምጽዋ በስተቀር በተቆጣጠረበት ወቅት፡ በምጽዋ አካባቢ የነበረው ጦር አፈግፍጎ በኢትዮጵያ የባሕር ኃይል መደብ በተጠጋበት ወቅት የባሕር ኃይላችንን የእግረኛ ጦር በማስተባበር መደቡ እንዳይያዝ የጦር መርከቦች የመድፍ ድጋፍ እየሰጡ እንዲዋጉ ሌትና ቀን በጀግንነት የመሩ እነደነበሩ በወቅቱ የነበሩት ይመሠክራሉ።

  • ከሃገር መከላከያና ከዋና የልዩ ልዩ ክፍል አዛዦች በአመራራቸው ላይ ተጽእኖ ሊያደርጉባቸው ሲሞካክሩ፡ ለማይመለከታቸው ነገር ሁሉ ተገቢ መልስ በመስጠት አመራራቸውን በተግባር ያሳዩ ውድ የኢትዮጵያ ሃገራችን ጀግና መኮንን ናቸው። በነበረው ስርአት ደስተኛ ባለመሆናቸውና ያልመሰላቸውን ነገር በድፍረት  ያለመቀበላቸው፡ ወደሚቀጥለው ማእርግ እንዲተላለፉ ያለመደረጉ፡ በተለይም የ1970 ው የአመራር ገድል የርሳቸው አመራር ሆኖ ሳለ፡ ሌሎች በሹመት ላይ ሹመት ሲደራረብላቸው የርሳቸውን ገድል ያዩ ሁሉ አለቆቻችን የሁልጊዜ ርእሰ ጉዳይ እንደነበር አይረሳኝም። ለወታደራዊ ከፍተኛ መኮንነታቸው ለተሰጣቸው ከባድ ኃላፊነት ከፍተኛ ጥንቃቄና በራሳቸው የሚተማመኑ ከመሆናቸው የተነሳ፡ ከምጽዋ ባሕር ኃይል መደብ ለሥራ ጉዳይ ወጥተው ሲመለሱ፡ በዋናው በር ላይ ያሉትን ዘቦች፡ እኔ እየነዳሁ ያለሁት መኪና መፈተሽ አለበት፤ ምናልባትም በጠላት ታፍኜ የባሕር ኃይሉ ግቢና በአካባቢው ያሉ የቆሙ ጦር መርከቦች ላይ ጠላት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በማለት ይናገራሉ፤ የጥቂት ስህተት ነገር፡ በጠላት መጠቃት እንደሚያመጣ ይናገሩና የሚያሳስቡና ባለግርማ ሞገስ ከፍተኛ መኮንን ናቸው።  ረጅም እድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ፡ ውድ ካፒቴን መርሻ ግርማ።

Picture
ክቡር ኮማንደር ማቴዎስ መኮንን ከባሕር ኃይላችን የማሪን ኢንጂነሪንግ ሲንየር መኮንኖች አንዱ ናቸው። ለሰባት አመታት ተኩል ባገለገልኩበት የ8ቱም ፈጣን አጥቂ ጦር መርከብ 111ኛ ስኳድሮን የማሪን ኢንጂነሪንግ ኮማንደር ሲሆኑ፡ የጦር መርከቦቹ ምንጊዜም ለግዳጅ ብቁ እንዲሆኑ፡ ከየጦር መርከቦቹ አባሎችን መርጠውና ሞባይል ቲም በማቋቋም የሶቪየት ሥሪት የሆኑትን የጦር መርከቦች ጥገና ሲያደርጉ ዕውቀታቸውን ሳይሸሽጉ በቲዎሪም ይሁን በተግባር ክልብ በሆነ ጥረት የሚያደርጉትን ሁሉ አብረዋቸው የሚሠሩት የማእርግ ጓደኞቼ ሁሉ በየዕለቱ ሲናገሩ የምንሰማው ሃቅ ነበር።


በተለይም የሶቪየት ጦር መርከቦች ኢንጂን EXPIRED DATE የተመደበለትና በአጋጣሚ ብልሽት ቢያጋጥመው እንኳን፡ እንደ ምራባውያኑ መለዋወጫ ተገጥሞለት እንደገና በሥራ ላይ እንዳይውል የተደረገ ስለነበር፡ ሁኔታው ከሚያሳስባቸው ቀዳሚ መኮንኖች አንዱ ስለነበሩ፡ አስታውሳለሁ በጦር መርከብ 162 ላይ GEAR BOX ላይ ችግር አለ በማለት SEALED ሆኖ የተገጠመውን ኢንጂን ከሌሎች የጦር መርከቦች ተፈታቶ ሜዳ ላይ ተቀምጦ ከነበሩት አስቸጋሪ የነበረው ውስብስብ በመፈታታት ለመርከባችን ጥገና አድርገው በብዙ ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣ የነበረውን ዋጋ ከአስተባበሩት የጥገና ቡድን ጋር ዓላማቸውን አሳክተዋል። ቀደም ብሎ ሁሉም የሶቪየት ጦር መርከቦች ነዳጃቸው በውድ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ስለነበር የሚገዛው፡ እንደሌሎቹ ከመራባውያን የተገዙት የጦር መርከቦች አሰብ ከሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ ነዳጃቸውን እንዲጠቀሙ፡ ከሌሎች መኮንኖች ጋር በመሆን ሁኔታውን አጥንተው ሃገራችንን ከኪሳራ ያዳኑና የሙያ አጋሮቻቸውና የማዕርግ ጓደኞቻችን፡ እውቀታቸውን በማካፈልም ሆነ ጉልበታቸውን ጭምር አብረው በመሥራት በተግባር  ሁልጊዜ በሚያደርጓቸው ከልብ የሆነ ትጋት፡ በማድነቅና በማክበር የሚያመሰግኗቸው ውድ የባሕር ኃይላችን ከፍተኛ መኮንን ናቸው።

 ---"""   ሌላው የእርሳቸው ትሩፋት፡ የባሕር ኃይላችን ጦር መርከቦች መደብ ወደ ዳሕላክ፤ ናኩራ ከተዛወረ በኋላ፡ በደሴቲቱ ላይ የውሃ ግድብ ባለመኖሩና በአካባቢው ያለው የባሕር ኃይልና የምድር ጦር ሠራዊት የውኃ ችግር በጣም የበረታበት ቦታ ስለሆነ፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከእስራኤል ሃገር የቀይ ባሕርን የጨው ውኃ ወደ ንጹሕ ውኃ የሚለውጥ ( DISTLLING PLANT) ታላቅ ፕሮጀክት እቅድን በተመለከተ፡ ለቀናት ብቻ እዚያው እስራኤል ሃገር ከውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ቴክኒሺያኖች ጋር ሄደው በእስራኤሎች በተደረገላቸው የጥቂት ቀናት ማብራሪያ ብቻ፡ ወደ ውድ ሃገራቸው እንደተመለሱ የ DISTLLING PLANT ቀደም ብሎ በሃገራችን ያልነበረ ቢሆንም፡ አብረዋቸው ለማብራሪያው እስራኤል ሃገር የነበሩት፡ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሠራተኞች ግዙፉ ፕሮጀክት ግራ አጋብቷቸው፡ ኮማንደር ማቴዎስን የሚሳካ ይመስለዎታልን ጥያቄ ሲአያስከትሉ፡ በአጋጣሚ የመጣው መሣሪያ ሁለት ቢሆንም፡ አንደኛው በንግድ መርከብ ጭነት ሲመጣ በማዕበል የተጎሻሸመና የተጎዳ ቢሆንም፡ ኮማንደሩ ባላቸው የዕውቀትም ይሁን የራስ ተነሳሽነት ፅናት ተደማምሮ መሣሪያው እንዲሠራና  ሁሉም ነገር ተሳክቶ የሠራዊቱንም ይሁን የአካባቢውን ሕዝብ የውኃ ፍላጎት አሳክተዋል። ኮማንደሬ ረጅም  ዕድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ """"
።