"
THE FORMER ETHIOPIAN NAVY MEMORIAL WEBSITE
  • THE FORMER ETHIOPIAN NAVY WEBSITE
  • ገጽ2
  • ገጽ3
  • ገጽ4
  • ገጽ 5
  • ገጽ 6
  • ገፅ 7

የኢትዮጵያን የወቅቱን ሃገር መከላከያ ሠራዊትን በተመለከተ

18/7/2020

0 Comments

 
 የኢትዮጵያ ሃገር መከላከያ ሠራዊት ተቋምን እና የክልል ኃይል ሥለሚባለው ቁልፍ ጉዳይ፡ ለጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አሕመድ የምለው ጉዳይ አለኝ። ይህ አመለካከቴ የአብዛኛው የቀድሞው ሠራዊት አባላትና የሃገራችን ጉዳይ በከፍተኛ ደረጃ ከሚያሣስባቸው ኢትዮጵያውያን ጋር የሚጋራ ሃገራዊ ኃላፊነት የሚሰማቸው ከዘር ፖለቲካ በፀዱ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሚንፀባረቅ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው። 
የሃገራችን የመከላከያ ሠራዊት ብቃት ከፍተኛ ነው እያሉ የሚናገሩትን የባሕላዊ ሹመት ላይ ባሉት የሠራዊቱ አመራሮች የሚናገሩትን ቃለ ምልልስ ማመን በጣም ይከብዳል፤ በበኩሌ ለመቀበል በጣም ይከብደኛል። አሁን ያለው የሃገር መከላከያ ሠራዊት የተተካው ቀደም ብሎ በደፈጣ ውጊያ ሃገር ሲያሸብሩት በነበሩት የሕወሃት የጫካ ወንበዴዎች አማካኝነት መሆኑ የአደባባይ ምሥጢር ነው። ከኤርትራ ጋር የሠላም ጎዳና ላይ ብንሆንም የእነዚህን ሽፍቶች ወታደራዊ ብቃት ለመገምገም የባድመ ጦርነትን ማስታወስ ግድ ይላል። እነ ስዬ አብርሃና ፃድቃን ገ/ተንሣይ የሚመሩት ጦር አብሯቸው ጫካ የነበረና ከላይ ከአመራሮቹ ከነፃድቃንና ስዬ አብርሃ ጀምሮ የደፈጣ ተዋጊና ምንም ሚሊታሪ ሳይንስ የማያውቁ የጫካ ቃፊሮች ከመሆናቸውም በላይ ሻቢያ ባድመን አልፎ እስከ ሽራሮ ድረስ ወረራ አድርጎ የሚመሩትን ታንክና ሠራዊት ድራሹን አጥፍቶ ሲወቅጣቸው የመከላከያ ሠራዊት ኤታ ሜጀር ሹም የተባለው ፃድቃን ገ/ተንሣይ እንደ እቃ አታስፈልጉም እኛ ጀግኖች ነን በማለት የጣሉዋቸውን የቀድሞውን ሠራዊት አባላት እባካችሁ ተወረርን ኧረ ድረሱልን ብለው አለቃቅሰው ለቀድሞው ሠራዊት ጥሪ ሲያደርጉ ፡ ከሠራዊቱ አባላት ከፍተኛ መኮንኖች " የሕብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግናው አየርወለድ ክቡር ጄኔራል ተስፋዬ ኃ/ማ ፤ ከምድርጦር  ክቡር ጄኔራል በኃይሉ ክንዴ ፤ ከአየር ኃይል የቀድሞው የአየር ኃይል ዘመቻ መኮንኑ ክቡር ጄኔራል ተጫኔ መስፍንና ሌሎችም በ 10,000 የሚቆጠሩ የቀድሞው ጦር አባላት ከታንከኛ ከመድፈኛና እግረኛ ተውጣጥተው አለን ለሃገራችን ኢትዮጵያ ብለው ሲደራጁም በመሃላቸው የወያኔ ንክኪ በጥባጭ እንዳይኖር ፃድቃንን አስጠንቅቀው ለአጭር ጊዜ አዲስ የተመለመሉ ወጣቶችን አሠልጥነው፤ እንዲሁም ምርጥ የአየር ኃይላችን የቀድሞው አብራሪዎችና ቴክኒሺያኖች በስደት ኡጋንዳ ፤ ጂቡቲና ኬንያ የነበሩት ጥሪ ሲደረግላቸው ምንም ሳያቅማሙ በቀላሉ ሻቢያን ማስተንፈስ እንደሚችሉ አውቀው ዘመቱ።
ያ ዘመቻ ለቀድሞው ጦር ቀላል ነበር ፤ ምክንያቱም በደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት ዘመን ሲዋጉ የነበረው ከአንድ አመፀኛ ወንበዴ ጋር ሳይሆን ከሶማሊያ ወራሪ ጦር ጋር በምሥራቅ ኢትዮጵያ ፤ በሰሜን ኤርትራ ውስጥና ትግራይ ውስጥ ከሻቢያ ፤ ጀብሃ ፤ አልዋህዳና ከወያኔ ጋር ፤ በወለጋ ከሱዳን ጦርና ከኦነግ ደፈጣ ወንበዴዎች ጋር ፤ በጎንደር ከኢዲዩ ጋር በመሃል ሃገር ከኢህአፓ ጋር....ወዘተርፈ ነበርና ይህ ጦርነት ለቀድሞው ሠራዊት ተኩስ አቁም ተብሎ የተፈረደበትን ቂም ለመወጣት ክንዱን ሻቢያ ላይ አሳይቶ በ 2 ቀናት ውስጥ ጦርነቱ ኤርትራ ውስጥ ነበር። የአየር ሃይላችን አባላት ለሁለት ዓመታት የተለዩዋቸውን ተዋጊ አይሮፕላኖች በጄኔራል ተጫነ መስፍን አመራር Refreshment Course አድርገው ተለማምደው ማንነታቸውን ማሳየታቸው አይዘነጋንም ወያኔ ታሪካቸውን ቢቀብረውም።
ወያኔዎች ሚዲያውን በሙሉ በራሳቸው ሥር ስላደረጉት የጄኔራል ተስፋዬ ኃ/ማርያምን አመራር ለወያኔ ሳሞራ የኑስ ፤ የጄኔራል በኃይሉ ክንዴን አመራር ለወያኔ ፃድቃን ገ/ተንሣይ ፤ የጄኔራል ተጫኔ መስፍንን አመራር ለወያኔ አበበ ተ/ኃይማኖት በማድረግ ድሉም አመራሩም የነርሱ እንደሆነ አድርገው ፕሮፓጋንዳ ነዙበት። በዛላንበሳ በኩል ሲመሩ የነበሩት ክቡር ጄኔራል ተሳፋዬ ኃ/ማ ሻቢያን ለማደናበር በሰው ቅርፅ የተሰራ አሻንጉሊት ውስጥ ፈንጂ እንዲደረግ አድርገው ሻቢያ ጦር መሃል እንዲወድቅ በፓራሹት እንዲወርድ ያደረጉበት ብልህ አመራር ውጤት ሻቢያዎች አየወለዶችን ከነሕይወት እንማርክ ብለው ፓራሹት ወራጆችን ተከትለው ያለቁበትን ታክቲክ ከባድ የነበረውን ዘመቻ በቀላሉ አሸንፈው ሠራዊቱ እስከ ሰንአፌ ድረስ ድል ማስገንዘቡን እናስታውሳለን፤ እርሳቸው ከኢሳት ሚዲያ ጋር በጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የተደረገላቸው ቃለ ምልልስ ላይም ዘግበውታል። ያ የባድመ የድሉ ዋነኛው ባለቤት የቀድሞው ጦር 10ኛ ክፍለጦር በሚል ተደራጅቶ ወያኔን ከውርደት ያዳነው ጦር በመለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንደገና ተበተነ። ዝርዝር ሁኔታውን ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ተገልጿል ፤ ዩትዩብ ላይ ታገኙታላችሁ።
ከላይ የዘረዘርኩት እውነታን ለወቅቱ መሪያችን ለጠቅላይ ሚንስትር አቢይና እርሱ ለሚመራቸው ለሲቪልና ለወታደራዊ አመራር ባለሥልጣኖች ማስታወሻ ምሳሌ እንዲሆን እንጂ አሁንም ከኤርትራ ጋር ጦርነት እናድርግ በሚል እሳቤ ምክንያት አይደለም ይህንን ማስታወሻ የፃፍኩትና፡ ጠ/ሚ አቢይ ይህንን ጉዳይ በጥልቀት አስቦ የታላላቅ ሃገራት መሪዎች እንኳን እነ አሜሪካና ሩሲያ አውሮፓ ታላላቅ ሃገራት መሪዎች ሥልጣን ሲረከቡ ዋና የደህንነትና የመከላከያ ሠራዊታቸውን የሚያማክሩት በአገልግሎት ላይ ያሉትን ከፍተኛ መኳንንትን ሳይሆን በልምድና ኣመራር ለረጅም ዘመናት በወታደራዊ አገልግሎት ዝና ያላቸውን ጡረታ ላይ ያሉትን ፊልድ ማርሻሎችን ፤ ጄኔራሎችን የቅርብ አማካሪዎች በማድረግ የሃገራቸውን ደህንነትና የመከላከያ ሠራዊታቸውን ብቃት ይገነባሉ። 

እነሆ ታዲያ ለጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አሕመድ የማመለክተው ጉዳይ የምታዘውን የመከላከያ ሠራዊት አዛዦች ሪፖርት ብቻ በመቀበል አትዘናጋ ? በቀድሞው ሠራዊት ልምድ ባላቸው ጄኔራሎች የመከላከያው ሠራዊቱን ብቃት ምን ያህል ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል አስገምግም ? ክቡር አየርወለድ ጄኔራል ተስፋዬ ኃ/ማ ፤ ክቡር የታንከኛና የሜካናይዝድ ተዋጊ ጦር ውጤታማው ጀግናው ጄኔራል ካሣዬ ጨመዳ ፤ በምሥራቁ ጦር ግምባር የወራሪውን የሶማሊያን ጦር በቦምብ ጣይ ጄት ተዋጊ አይሮፕላን በማብረር ዳይቭ እየገቡ ካደባዩት ምርጥ የአየር ኃይላችን አብራሪውን ጄኔራል ተጫኔ መስፍንን ወታደራዊ ሳይንስ እውቀታቸውን እንዲያካፍሉ እባክህ በአማካሪነትና መሠረታዊ እውቀታቸውንና ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ አቅርባቸው ፤ መልካም ጥሪም አድርግላቸው።

ፍሬሠናይ ከበደ
0 Comments

    ገፅ 7

    All

    RSS Feed

Picture
Picture
  •  ክቡር ካፒቴን መርሻ ግርማ ፡ ከባሕር ኃይላችን ሲንየር የባሕር ኃይል መኮንኖች አንዱ ሲሆኑ፡ እውቀታቸውን ከድፍረታቸው ጋር በራስ የመተማመን ባሕርያቸው ጋር ከምክትል የጦር መርከብ አዛዥነት እሰከዋና አዛዥነት ሃገራቸው ኢትዮጵያን በጀግንነት አገልግለዋል። በባሕር ኃይል አባልነት ከተቀጠርን ጊዜያት አንስቶ በ1970 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር የነበሩት አለቆቻችን ሲናገሩ፡ ጠላት የሻቢያ ጦር መላውን ኤርትራ ከአሥመራና ከምጽዋ በስተቀር በተቆጣጠረበት ወቅት፡ በምጽዋ አካባቢ የነበረው ጦር አፈግፍጎ በኢትዮጵያ የባሕር ኃይል መደብ በተጠጋበት ወቅት የባሕር ኃይላችንን የእግረኛ ጦር በማስተባበር መደቡ እንዳይያዝ የጦር መርከቦች የመድፍ ድጋፍ እየሰጡ እንዲዋጉ ሌትና ቀን በጀግንነት የመሩ እነደነበሩ በወቅቱ የነበሩት ይመሠክራሉ።

  • ከሃገር መከላከያና ከዋና የልዩ ልዩ ክፍል አዛዦች በአመራራቸው ላይ ተጽእኖ ሊያደርጉባቸው ሲሞካክሩ፡ ለማይመለከታቸው ነገር ሁሉ ተገቢ መልስ በመስጠት አመራራቸውን በተግባር ያሳዩ ውድ የኢትዮጵያ ሃገራችን ጀግና መኮንን ናቸው። በነበረው ስርአት ደስተኛ ባለመሆናቸውና ያልመሰላቸውን ነገር በድፍረት  ያለመቀበላቸው፡ ወደሚቀጥለው ማእርግ እንዲተላለፉ ያለመደረጉ፡ በተለይም የ1970 ው የአመራር ገድል የርሳቸው አመራር ሆኖ ሳለ፡ ሌሎች በሹመት ላይ ሹመት ሲደራረብላቸው የርሳቸውን ገድል ያዩ ሁሉ አለቆቻችን የሁልጊዜ ርእሰ ጉዳይ እንደነበር አይረሳኝም። ለወታደራዊ ከፍተኛ መኮንነታቸው ለተሰጣቸው ከባድ ኃላፊነት ከፍተኛ ጥንቃቄና በራሳቸው የሚተማመኑ ከመሆናቸው የተነሳ፡ ከምጽዋ ባሕር ኃይል መደብ ለሥራ ጉዳይ ወጥተው ሲመለሱ፡ በዋናው በር ላይ ያሉትን ዘቦች፡ እኔ እየነዳሁ ያለሁት መኪና መፈተሽ አለበት፤ ምናልባትም በጠላት ታፍኜ የባሕር ኃይሉ ግቢና በአካባቢው ያሉ የቆሙ ጦር መርከቦች ላይ ጠላት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በማለት ይናገራሉ፤ የጥቂት ስህተት ነገር፡ በጠላት መጠቃት እንደሚያመጣ ይናገሩና የሚያሳስቡና ባለግርማ ሞገስ ከፍተኛ መኮንን ናቸው።  ረጅም እድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ፡ ውድ ካፒቴን መርሻ ግርማ።

Picture
ክቡር ኮማንደር ማቴዎስ መኮንን ከባሕር ኃይላችን የማሪን ኢንጂነሪንግ ሲንየር መኮንኖች አንዱ ናቸው። ለሰባት አመታት ተኩል ባገለገልኩበት የ8ቱም ፈጣን አጥቂ ጦር መርከብ 111ኛ ስኳድሮን የማሪን ኢንጂነሪንግ ኮማንደር ሲሆኑ፡ የጦር መርከቦቹ ምንጊዜም ለግዳጅ ብቁ እንዲሆኑ፡ ከየጦር መርከቦቹ አባሎችን መርጠውና ሞባይል ቲም በማቋቋም የሶቪየት ሥሪት የሆኑትን የጦር መርከቦች ጥገና ሲያደርጉ ዕውቀታቸውን ሳይሸሽጉ በቲዎሪም ይሁን በተግባር ክልብ በሆነ ጥረት የሚያደርጉትን ሁሉ አብረዋቸው የሚሠሩት የማእርግ ጓደኞቼ ሁሉ በየዕለቱ ሲናገሩ የምንሰማው ሃቅ ነበር።


በተለይም የሶቪየት ጦር መርከቦች ኢንጂን EXPIRED DATE የተመደበለትና በአጋጣሚ ብልሽት ቢያጋጥመው እንኳን፡ እንደ ምራባውያኑ መለዋወጫ ተገጥሞለት እንደገና በሥራ ላይ እንዳይውል የተደረገ ስለነበር፡ ሁኔታው ከሚያሳስባቸው ቀዳሚ መኮንኖች አንዱ ስለነበሩ፡ አስታውሳለሁ በጦር መርከብ 162 ላይ GEAR BOX ላይ ችግር አለ በማለት SEALED ሆኖ የተገጠመውን ኢንጂን ከሌሎች የጦር መርከቦች ተፈታቶ ሜዳ ላይ ተቀምጦ ከነበሩት አስቸጋሪ የነበረው ውስብስብ በመፈታታት ለመርከባችን ጥገና አድርገው በብዙ ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣ የነበረውን ዋጋ ከአስተባበሩት የጥገና ቡድን ጋር ዓላማቸውን አሳክተዋል። ቀደም ብሎ ሁሉም የሶቪየት ጦር መርከቦች ነዳጃቸው በውድ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ስለነበር የሚገዛው፡ እንደሌሎቹ ከመራባውያን የተገዙት የጦር መርከቦች አሰብ ከሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ ነዳጃቸውን እንዲጠቀሙ፡ ከሌሎች መኮንኖች ጋር በመሆን ሁኔታውን አጥንተው ሃገራችንን ከኪሳራ ያዳኑና የሙያ አጋሮቻቸውና የማዕርግ ጓደኞቻችን፡ እውቀታቸውን በማካፈልም ሆነ ጉልበታቸውን ጭምር አብረው በመሥራት በተግባር  ሁልጊዜ በሚያደርጓቸው ከልብ የሆነ ትጋት፡ በማድነቅና በማክበር የሚያመሰግኗቸው ውድ የባሕር ኃይላችን ከፍተኛ መኮንን ናቸው።

 ---"""   ሌላው የእርሳቸው ትሩፋት፡ የባሕር ኃይላችን ጦር መርከቦች መደብ ወደ ዳሕላክ፤ ናኩራ ከተዛወረ በኋላ፡ በደሴቲቱ ላይ የውሃ ግድብ ባለመኖሩና በአካባቢው ያለው የባሕር ኃይልና የምድር ጦር ሠራዊት የውኃ ችግር በጣም የበረታበት ቦታ ስለሆነ፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከእስራኤል ሃገር የቀይ ባሕርን የጨው ውኃ ወደ ንጹሕ ውኃ የሚለውጥ ( DISTLLING PLANT) ታላቅ ፕሮጀክት እቅድን በተመለከተ፡ ለቀናት ብቻ እዚያው እስራኤል ሃገር ከውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ቴክኒሺያኖች ጋር ሄደው በእስራኤሎች በተደረገላቸው የጥቂት ቀናት ማብራሪያ ብቻ፡ ወደ ውድ ሃገራቸው እንደተመለሱ የ DISTLLING PLANT ቀደም ብሎ በሃገራችን ያልነበረ ቢሆንም፡ አብረዋቸው ለማብራሪያው እስራኤል ሃገር የነበሩት፡ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሠራተኞች ግዙፉ ፕሮጀክት ግራ አጋብቷቸው፡ ኮማንደር ማቴዎስን የሚሳካ ይመስለዎታልን ጥያቄ ሲአያስከትሉ፡ በአጋጣሚ የመጣው መሣሪያ ሁለት ቢሆንም፡ አንደኛው በንግድ መርከብ ጭነት ሲመጣ በማዕበል የተጎሻሸመና የተጎዳ ቢሆንም፡ ኮማንደሩ ባላቸው የዕውቀትም ይሁን የራስ ተነሳሽነት ፅናት ተደማምሮ መሣሪያው እንዲሠራና  ሁሉም ነገር ተሳክቶ የሠራዊቱንም ይሁን የአካባቢውን ሕዝብ የውኃ ፍላጎት አሳክተዋል። ኮማንደሬ ረጅም  ዕድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ """"
።