"
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል መታሰቢያ ዌብሳይት ETHIOPIAN NAVY MEMORIAL WEBSITE
  • ገጽ 1
    • ገጽ2
  • ገጽ2

    Author

    Write something about yourself. No need to be fancy, just an overview.

    Archives

    No Archives

    Categories

    All

    RSS Feed

Picture
Picture
  •  ክቡር ካፒቴን መርሻ ግርማ ፡ ከባሕር ኃይላችን ሲንየር የባሕር ኃይል መኮንኖች አንዱ ሲሆኑ፡ እውቀታቸውን ከድፍረታቸው ጋር በራስ የመተማመን ባሕርያቸው ጋር ከምክትል የጦር መርከብ አዛዥነት እሰከዋና አዛዥነት ሃገራቸው ኢትዮጵያን በጀግንነት አገልግለዋል። በባሕር ኃይል አባልነት ከተቀጠርን ጊዜያት አንስቶ በ1970 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር የነበሩት አለቆቻችን ሲናገሩ፡ ጠላት የሻቢያ ጦር መላውን ኤርትራ ከአሥመራና ከምጽዋ በስተቀር በተቆጣጠረበት ወቅት፡ በምጽዋ አካባቢ የነበረው ጦር አፈግፍጎ በኢትዮጵያ የባሕር ኃይል መደብ በተጠጋበት ወቅት የባሕር ኃይላችንን የእግረኛ ጦር በማስተባበር መደቡ እንዳይያዝ የጦር መርከቦች የመድፍ ድጋፍ እየሰጡ እንዲዋጉ ሌትና ቀን በጀግንነት የመሩ እነደነበሩ በወቅቱ የነበሩት ይመሠክራሉ።

  • ከሃገር መከላከያና ከዋና የልዩ ልዩ ክፍል አዛዦች በአመራራቸው ላይ ተጽእኖ ሊያደርጉባቸው ሲሞካክሩ፡ ለማይመለከታቸው ነገር ሁሉ ተገቢ መልስ በመስጠት አመራራቸውን በተግባር ያሳዩ ውድ የኢትዮጵያ ሃገራችን ጀግና መኮንን ናቸው። በነበረው ስርአት ደስተኛ ባለመሆናቸውና ያልመሰላቸውን ነገር በድፍረት  ያለመቀበላቸው፡ ወደሚቀጥለው ማእርግ እንዲተላለፉ ያለመደረጉ፡ በተለይም የ1970 ው የአመራር ገድል የርሳቸው አመራር ሆኖ ሳለ፡ ሌሎች በሹመት ላይ ሹመት ሲደራረብላቸው የርሳቸውን ገድል ያዩ ሁሉ አለቆቻችን የሁልጊዜ ርእሰ ጉዳይ እንደነበር አይረሳኝም። ለወታደራዊ ከፍተኛ መኮንነታቸው ለተሰጣቸው ከባድ ኃላፊነት ከፍተኛ ጥንቃቄና በራሳቸው የሚተማመኑ ከመሆናቸው የተነሳ፡ ከምጽዋ ባሕር ኃይል መደብ ለሥራ ጉዳይ ወጥተው ሲመለሱ፡ በዋናው በር ላይ ያሉትን ዘቦች፡ እኔ እየነዳሁ ያለሁት መኪና መፈተሽ አለበት፤ ምናልባትም በጠላት ታፍኜ የባሕር ኃይሉ ግቢና በአካባቢው ያሉ የቆሙ ጦር መርከቦች ላይ ጠላት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በማለት ይናገራሉ፤ የጥቂት ስህተት ነገር፡ በጠላት መጠቃት እንደሚያመጣ ይናገሩና የሚያሳስቡና ባለግርማ ሞገስ ከፍተኛ መኮንን ናቸው።  ረጅም እድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ፡ ውድ ካፒቴን መርሻ ግርማ።

Picture
ክቡር ኮማንደር ማቴዎስ መኮንን ከባሕር ኃይላችን የማሪን ኢንጂነሪንግ ሲንየር መኮንኖች አንዱ ናቸው። ለሰባት አመታት ተኩል ባገለገልኩበት የ8ቱም ፈጣን አጥቂ ጦር መርከብ 111ኛ ስኳድሮን የማሪን ኢንጂነሪንግ ኮማንደር ሲሆኑ፡ የጦር መርከቦቹ ምንጊዜም ለግዳጅ ብቁ እንዲሆኑ፡ ከየጦር መርከቦቹ አባሎችን መርጠውና ሞባይል ቲም በማቋቋም የሶቪየት ሥሪት የሆኑትን የጦር መርከቦች ጥገና ሲያደርጉ ዕውቀታቸውን ሳይሸሽጉ በቲዎሪም ይሁን በተግባር ክልብ በሆነ ጥረት የሚያደርጉትን ሁሉ አብረዋቸው የሚሠሩት የማእርግ ጓደኞቼ ሁሉ በየዕለቱ ሲናገሩ የምንሰማው ሃቅ ነበር።


በተለይም የሶቪየት ጦር መርከቦች ኢንጂን EXPIRED DATE የተመደበለትና በአጋጣሚ ብልሽት ቢያጋጥመው እንኳን፡ እንደ ምራባውያኑ መለዋወጫ ተገጥሞለት እንደገና በሥራ ላይ እንዳይውል የተደረገ ስለነበር፡ ሁኔታው ከሚያሳስባቸው ቀዳሚ መኮንኖች አንዱ ስለነበሩ፡ አስታውሳለሁ በጦር መርከብ 162 ላይ GEAR BOX ላይ ችግር አለ በማለት SEALED ሆኖ የተገጠመውን ኢንጂን ከሌሎች የጦር መርከቦች ተፈታቶ ሜዳ ላይ ተቀምጦ ከነበሩት አስቸጋሪ የነበረው ውስብስብ በመፈታታት ለመርከባችን ጥገና አድርገው በብዙ ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣ የነበረውን ዋጋ ከአስተባበሩት የጥገና ቡድን ጋር ዓላማቸውን አሳክተዋል። ቀደም ብሎ ሁሉም የሶቪየት ጦር መርከቦች ነዳጃቸው በውድ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ስለነበር የሚገዛው፡ እንደሌሎቹ ከመራባውያን የተገዙት የጦር መርከቦች አሰብ ከሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ ነዳጃቸውን እንዲጠቀሙ፡ ከሌሎች መኮንኖች ጋር በመሆን ሁኔታውን አጥንተው ሃገራችንን ከኪሳራ ያዳኑና የሙያ አጋሮቻቸውና የማዕርግ ጓደኞቻችን፡ እውቀታቸውን በማካፈልም ሆነ ጉልበታቸውን ጭምር አብረው በመሥራት በተግባር  ሁልጊዜ በሚያደርጓቸው ከልብ የሆነ ትጋት፡ በማድነቅና በማክበር የሚያመሰግኗቸው ውድ የባሕር ኃይላችን ከፍተኛ መኮንን ናቸው።

 ---"""   ሌላው የእርሳቸው ትሩፋት፡ የባሕር ኃይላችን ጦር መርከቦች መደብ ወደ ዳሕላክ፤ ናኩራ ከተዛወረ በኋላ፡ በደሴቲቱ ላይ የውሃ ግድብ ባለመኖሩና በአካባቢው ያለው የባሕር ኃይልና የምድር ጦር ሠራዊት የውኃ ችግር በጣም የበረታበት ቦታ ስለሆነ፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከእስራኤል ሃገር የቀይ ባሕርን የጨው ውኃ ወደ ንጹሕ ውኃ የሚለውጥ ( DISTLLING PLANT) ታላቅ ፕሮጀክት እቅድን በተመለከተ፡ ለቀናት ብቻ እዚያው እስራኤል ሃገር ከውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ቴክኒሺያኖች ጋር ሄደው በእስራኤሎች በተደረገላቸው የጥቂት ቀናት ማብራሪያ ብቻ፡ ወደ ውድ ሃገራቸው እንደተመለሱ የ DISTLLING PLANT ቀደም ብሎ በሃገራችን ያልነበረ ቢሆንም፡ አብረዋቸው ለማብራሪያው እስራኤል ሃገር የነበሩት፡ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሠራተኞች ግዙፉ ፕሮጀክት ግራ አጋብቷቸው፡ ኮማንደር ማቴዎስን የሚሳካ ይመስለዎታልን ጥያቄ ሲአያስከትሉ፡ በአጋጣሚ የመጣው መሣሪያ ሁለት ቢሆንም፡ አንደኛው በንግድ መርከብ ጭነት ሲመጣ በማዕበል የተጎሻሸመና የተጎዳ ቢሆንም፡ ኮማንደሩ ባላቸው የዕውቀትም ይሁን የራስ ተነሳሽነት ፅናት ተደማምሮ መሣሪያው እንዲሠራና  ሁሉም ነገር ተሳክቶ የሠራዊቱንም ይሁን የአካባቢውን ሕዝብ የውኃ ፍላጎት አሳክተዋል። ኮማንደሬ ረጅም  ዕድሜና ጤንነት እመኝሎታለሁ """"
።